Mon Jun 19 2017 18:20:35 GMT+0300 (E. Africa Standard Time)
This commit is contained in:
parent
effafc057c
commit
c90546be21
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 12 \v 1 \v 2 \v 3 1 ስለ እስራኤል የተነገረው የያህዌ ቃል ዐዋጅ ይህ ነው። ሰማያትን የዘረጋ፣ ምድርን የመሠረተ፣ የሰውን መንፈስ የሠራ ያህዌ እንዲህ ይላል፣ 2 “ኢየሩሳሌምን በዙሪያዋ ያሉትን ሕዝቦች ሁሉ የሚያንገዳግድ ጽዋ አደርጋታለሁ። ኢየሩሳሌም በምትከበብበት ጊዜ ይሁዳም ላይ እንደዚያው ይሆናል። 3 በዚያ ቀን ኢየሩሳሌምን አሕዛብ ሁሉ ላይ ከባድ ድንጋይ አደርጋታለሁ። ያንን ድንጋይ ማንቀሳቀስ የሚሞክር ሁሉ ክፉኛ ይጎዳል፤ የምድር ሕዝቦች ሁሉ በዚያች ከተማ ላይ ይሰበሰባሉ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 4 \v 5 4 በዚያ ቀን፣ ፍረሱን ሁሉ በሽብር፣ የተቀመጠበትንም ሁሉ በእብደት እመታለሁ። የይሁዳን ቤት በምሕረት አያለሁ፤ የጠላትን ፈረስ ሁሉ አሳውራለሁ። 5 በዚያ ጊዜ የይሁዳ መሪዎች በልባቸው፣ የሰራዊት ጌታ ያህዌ አምላካቸው ስለ ሆነ የኢየሩሳሌም ሕዝቦች ብርታታችን ናቸው!” ይላሉ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 6 6 በዚያ ቀን የይሁዳን መሪዎች በእንጨት ክምር ውስጥ እንዳለ የእሳት ምድጃ በነዶም መካከል እንዳለ ችቦ ነበልባል አደርጋለሁ፤ በቀኝና በግራ ዙሪያውን ያሉትን ሕዝቦች ይበላሉ፤ ኢየሩሳሌምም እንደ ገና ከምድሯ ትኖራልች።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 7 \v 8 \v 9 7 የዳዊት ቤትና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ክብር ከይሁዳ ክብር እንዳይበልጥ፣ በዚያ ቀን ያህዌ በመጀመሪያ የይሁዳን መኖሪያዎች ያድናል። 8 በዚያ ቀን ያህዌ የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ከለላ ይሆናል፤ በዚያ ቀን በመካከላቸው ያለው ደካማው እንደ ዳዊት፣ የዳዊት ቤትም በፊታቸው እንደ አምላክ፣ እንደ ያህዌም መልአክ ይሆናል። 9 በዚያ ቀን ኢየሩሳሌም ላይ የሚነሡ ሕዝቦችን ሁሉ ማጥፋት እጀምራለሁ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 10 \v 11 10 በዚያ ቀን በዳዊት ቤትና በኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ላይ የርኅራኄና የልመናን መንፈስ አፈስሳለሁ፣ ወደ ወጉኝ ወደ እኔ ይመለክታሉ፤ እነርሱም ለአንድ ልጁ እንደሚያለቅስ ሰው ያለቅሱልኛል፤ ለበኩር ልጁ ሞት እንደሚያለቅስ ሰው ምርር ብለው ያለቅሳሉ። 11 በዚያ ቀን ኢየሩሳሌም ውስጥ የሚሆነው ለቅስ በመጊዶ ሜዳ ለሐዳድ ሪሞን እንደ ተለቀሰው ታላቅ ለቅሶ ይሆናል።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 12 \v 13 \v 14 12 ምድሪቱ ታለቅሳለች፤ የእያንዳንዱ ወገን ቤተ ሰብ ለየራሱ ያለቅሳል። የዳዊት ቤት ወገን ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ የናታን ቤት ወገን ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ 13 የሌዊ ቤት ወገን ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ የሰማኢ ቤት ወገን ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ 14 የቀሩትም ወገኖች ወንዶች ሁሉ ከነሚስቶቻቸው ያለቅሳሉ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 13 \v 1 \v 2 1 በዚያ ቀን የዳዊትን ቤትና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎችን ኀጢአትና ርኵሰት የሚያነጻ ምንጭ ይከፈታል። 2 በዚያ ቀን ከእንግዲህ አስታዋሽ እንዳይኖራቸው የጣዖቶችን ስሞች ከምድሪቱ አጠፋለሁ ይላል የሰራዊት ጌታ ያህዌ። ሐሰተኛ ነቢያትንና ርኵሳን መናፍስቶቻቸውም ከምድሪቱ ይወገዳሉ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 3 3 ማንም ትንቢት ቢናገር ወላጅ አባት እናቱ፣ “በያህዌ ስም ሐሰት ተናግረሃልና ትሞታለህ!” ይሉታል። ትንቢት ሲናገርም የገዛ ወላጆቹ ይወጉታል።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 4 \v 5 \v 6 4 በዚያ ቀን እያንዳንዱ ነቢይ ስለሚናገረው ትንቢት ራእይ ያፍራል። እነዚህ ነቢያት ሕዝቡን ለማታለል ከእንግዲህ ጠጕራም ልብስ አይለብስም። እያንዳንዱ፣ “እኔ ገበሬ እንጂ፣ ነቢይ አይደለሁም፤ ከልጅነቴ ጀምሮ ኑርዬ የተመሠረተውም በዚሁ ነበር!” ይላል። 6 ሌላውም መልሶ፣ “ታዲያ፣ ክንዶችህ” መካከል ያሉት እነዚህ ቁስሎች ምንድናቸው?” በማለት ቢጠይቀው፣ “በባልንጀሮቼ ቤት ሳለሁ ያቆሰልሁት ነው” በማለት ይመልሳል።
|
Loading…
Reference in New Issue