\c 9 \v 1 አምስተኛው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ እኔም ከሰማይ ወደ ምድር ወደቆ የነበረውን ኮከብ አየሁ። ለኮከቡም ወደ ሙታን ዓለም የሚያወርደውን ጉድጓድ መክፈቻ እግዚአብሔር ሰጠው። \v 2 ጉድጓዱን ሲከፍተው ከታላቅ ምድጃ እንደሚወጣ ዐይነት ጢስ ወጣ። ጢሱ የፀሐይን ብርሃንና ሰማይን ከማየት ጋረደ።