\c 17 \v 1 ሰባቱን ጽዋዎች ከያዙ ሰባት መላእክት አንዱ ወደ እኔ መጥቶ፣ “ና እግዚአብሔር አመንዝራዋን፣ ብዙ ውሆች ያሉበትን ከተማ የምትወክለውን ሴት፣ እንዴት እንደሚቀጣ አሳይሃለሁ። \v 2 የምድር ነገሥታት ከእርሷ ጋር አመንዘሩ፤ ጣዖትንም አመለኩ። በምድር የሚኖሩ ሰዎችም ይህንኑ አደረጉ። ድርጊታቸው እርሷ በሰጠቻቸው ወይን ጠጅ እንደ መስከር ሆነ” አለኝ።