\c 15 \v 1 በጣም እንግዳና ያልተለመደ ነገር በሰማይ አየሁ። ሰባት መላእክትን አየሁ፤ ሥራቸውም በሰባት የተለያዩ መንገዶች ዐመፀኞችን መቅጣት ነበር። እግዚአብሔር በዐመፀኞች በጣም በመቆጣቱ ከኃጢአተኛ ሕይወታቸው እንዲመለሱ ዕድል ለመስጠት ይህ ለመጨረሻ የሚቀጡበት ጊዜ ነው።