diff --git a/03/05.txt b/03/05.txt new file mode 100644 index 0000000..b8026dc --- /dev/null +++ b/03/05.txt @@ -0,0 +1 @@ +\v 5 ሰይጣንን ያሸነፉ ይህን የመሰለ ነጭ ልብስ ይለብሳሉ። የዘላለም ሕይወት ያላቸው ሰዎችን ስሞች ከያዘው የሕይወት መጽሐፍ ስማቸውን አልደመስስም። ይልቁንም፣ የእኔ መሆናቸውን በአባቴና በመላእክቱ ፊት እመሰክርላቸዋለሁ። \v 6 መረዳት የሚፈልግ ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር መንፈስ የሚናገረውን በጥንቃቄ መስማት አለበት።” \ No newline at end of file diff --git a/03/07.txt b/03/07.txt new file mode 100644 index 0000000..0f75929 --- /dev/null +++ b/03/07.txt @@ -0,0 +1 @@ +\v 7 “ለፊላድልፍያ ከተማ ቤተ ክርስቲያን ይህን መልእክት ጻፍ፤ እነዚህን ነገሮች ለአንተ እናገራለሁ። እኔ ቅዱሱ ነኝ፤ እውነተኛው ነኝ። ንጉሥ ዳዊት ሰዎች ወደ ጥንቱ የኢየሩሳሌም ከተማ እንዲገቡ የመፍቀድ ሥልጣን እንደ ነበረው፤ እኔም ሰዎች ወደ መንግሥቴ እንዲገቡ የመፍቀድ ሥልጣን አለኝ። ማንም እንዳይዘጋው አድርጌ በር የምከፍት፣ ማንም እንዳይከፍተው አድርጌ በር የምዘጋ እኔ ነኝ። \v 8 ያደረግኸውን ሁሉ አውቃለሁ። ማንም መዝጋት የማይችለውን በር በፊትህ ከፍቻለሁና ልብ በል። ኃይልህ በጣም ትንሽ ቢሆንም፣ እንደ ታዘዝከኝ አውቃለሁ፤ በእኔ ማመንህን አልካድህም። \ No newline at end of file diff --git a/03/09.txt b/03/09.txt new file mode 100644 index 0000000..ce4c2e5 --- /dev/null +++ b/03/09.txt @@ -0,0 +1 @@ +\v 9 ከእናንተ አንዳንዶቹ ሰይጣንን ከሚከተሉ ጋር እንደሚገናኙ አውቃለሁ። አይሁድ ነን ይላሉ፤ ግን በእውነት አይሁድ እንዳይደሉ አውቃለሁ። ሐሰተኞች ናቸው። ወደ አንተ መጥተው ዝቅ ብለው እግርህ ሥር እንዲወድቁና እኔ እንደ ወደድሁህ እንዲመሰክሩ አደርጋቸዋለሁ። \v 10 መከራን በትዕግሥት እንድትቀበል ለሰጠሁህ ትእዛዝ ስለ ታዘዝህ፣ እኔ ላይ እንድታምፅ ሊያደርጉህ ከሚሞክሩ እጠብቅሃለሁ። በመላው ዓለም ባሉት ሁሉ ላይ በቅርቡ ይህን ያደርጋሉ። \v 11 እኔ ቶሎ እመጣለሁ። ስለዚህ ማንም እግዚአብሔር ያዘጋጀልህን ሽልማት እንዳያሳጣህ፣ እኔ የነገርሁህን በማድረግ ጽና። \ No newline at end of file diff --git a/manifest.json b/manifest.json index 7c43b86..4c7a17f 100644 --- a/manifest.json +++ b/manifest.json @@ -58,6 +58,9 @@ "02-24", "02-26", "03-01", - "03-03" + "03-03", + "03-05", + "03-07", + "03-09" ] } \ No newline at end of file