\v 5 ሰዎቹ ግን ግብዣውን ከልብ አልተቀበሉትም፡፡ አንዳንዶቹ ወደ እርሻዎቻቸው፣ ሌሎች ደግሞ ወደ ሥራ ቦታቸው ሄዱ፡፡ \v 6 አንዳንዶቹ የንጉሡን አገልጋዮች ደበደቡዋቸው፤ አዋረዱዋቸው፤ ገደሉዋቸው፡፡ \v 7 ንጉሡ በጣም ስለ ተቆጣ፤ ወታደሮቹን ላከ፤ እነዚያን ሰዎች ገደለ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ፡፡