Wed Jul 05 2017 12:02:26 GMT+0300 (E. Africa Standard Time)
This commit is contained in:
parent
5f9f36d7a0
commit
c69e57c1fa
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 21 \v 1 \v 2 \v 3 1 ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሩሳሌም ሲቀርቡ፣ በደብረ ዘይት ወዳለው ወደ ቤተፋጌ መጡ፤ 2 ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ በማለት ሁለት ደቀ መዛሙርት ላከ፦ “ወደሚቀጥለው መንደር ሂዱ፤ አህያም ከነውርንጫዋ ታስራ ታገኛላችሁ። ፈትታችሁ ወደ እኔ አምጧቸው፤ 3 ማንም ስለዚያ አንዳች ቢናገራችሁ፤ እርሱም ከእናንተ ጋር ፈጥኖ ይሰዳቸዋል።”
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 4 \v 5 4 ይህ የሆነው፣5“እነሆ፣ ንጉሥሽ ትሑት ሆኖ በአህያና በውርንጫዋ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል ብላችሁ ለጽዮን ልጅ ንገሯት” ተብሎ በነብዩ የተተነበየው ይፈጸም ዘንድ ነው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 6 \v 7 \v 8 6ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ሄደው ልክ ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ። 7 አህያይቱንና ውርንጫዋን አመጡ፤ ልብሳቸውንም አደረጉባቸውና ኢየሱስ ተቀመጠባቸው። 8 ከሕዝቡ አብዛኞቹ ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፣ ሌሎችም የዘንባባ ዝንጣፊ እየቆረጡ በመንገድ ላይ አደረጉ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 9 \v 10 \v 11 9 ከኢየሱስ ፊት ይሄዱ የነበሩትና የተከተሉትም ሕዝብ፣ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ እርሱ የተባረከ ነው። ሆሣዕና በአርያም ይሁን!” በማለት ጮኹ። 10 ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም በመጣ ጊዜ ከተማይቱ በሞላ ታወከችና፣ “ይህ ማን ነው?” አለች። 11 ሕዝቡ፣ “ይህ ከገሊላ ናዝሬት የሆነው ነቢይ ኢየሱስ ነው” ብለው መለሱ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 12 \v 13 \v 14 12 ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሄደ። በቤተ መቅደስ የሚሸጡትንና የሚገዙትን አስወጣ። የገንዘብ ለዋጮችን ጠረጴዛዎችና ወንበሮች ገለበጠ። 13 እንዲህም አላቸው፦ ‘ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል’ ተብሎ ተጽፏል። እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት። 14 ከዚያም ዐይነ ስውሮችና ሽባዎች ወደ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ መጡ፤ እርሱም ፈወሳቸው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 15 \v 16 \v 17 15 ነገር ግን የካህናት አለቆችና የሕግ መምህራን እርሱ ያደረጋቸውን ድንቅ ነገሮች ባዩና በቤተ መቅደስ ልጆች፣ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ” በማለት ሲጮኹ በሰሙ ጊዜ፣ ተቆጡ። 16 “ሕዝቡ የሚሉትን ትሰማለህን?” አሉት። ኢየሱስ፣ “አዎ! ነገር ግን ‘ከሕፃናትና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ’ የሚለውን ከቶ አላነበባችሁምን?” አላቸው። 17 ከዚያም ኢየሱስ ትቷቸው ከከተማው ወጣና ወደ ቢታንያ ሄደ በዚያ ዐደረ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 18 \v 19 18 ኢየሱስ ጠዋት ወደ ከተማው ሲመለስ፣ ተራበ፦ 19 በመንገድ ዳር አንዲት የበለስስ ተክል አየና ወደ እርሷ ሄደ፤ ነገር ግን ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም። “ሁለተኛ ከቶ ፍሬ አይገኝብሽ” አላት። የበለስ ተክሊቱም ወዲያውኑ ደረቀች።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 20 \v 21 \v 22 2 ደቀ መዛሙርቱ ባዩአት ጊዜ ተደንቀው፣ “የበለስ ተክሊቱ እንዴት ወዲያውኑ ደረቀች?” አሉ። ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፦”በእውነት እላችኋለሁ፣ እምነት ቢኖራችሁና ባትጠራጠሩ፣ በዚች የበለስ ተክል የሆነባትን ብቻ ሳይሆን፤ይህን ኮረብታ ከዚህ ተነሥተህ ወደ ባሕር ተወርወር እንኳ ብትሉት ይፈጸማል። 22 አምናችሁ በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ።”
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 23 \v 24 23ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ሲያስተምር የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ወደ እርሱ መጥተው፣ “በምን ሥልጣን እነዚህን ነገሮች ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?” አሉ። 24 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፦ “እኔ ደግሞ አንድ ጥያቄ እጠይቃችኋለሁ። ያንን ከነገራችሁኝ እኔ ደግሞ በማን ሥልጣን እነዚህን ነገሮች እንደማደርግ እነግራችኋለሁ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 25 \v 26 \v 27 25 የዩሐንስ ጥምቀት ከየት መጣ ከሰማይ ነውን ወይስ ከሰዎች?” እርስ በርሳቸው እንዲህ በማለት ተነጋገሩ፦ “ከሰማይ ነው ብንለው፣ ‘ለምን አታምኑትም?’ ይለናል። 26 ነገር ግን ‘ከሰው ነው ብንል፣ ዮሐንስን እንደ ነቢይ ስለሚያዩት ሕዝቡን እንፈራለን።” 27 ከዚያም መልሰው ኢየሱስን፣ “አናውቅም” አሉት። እርሱ ደግሞ፣ “እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን ነገሮች እንደማደርግ አልነግራችሁም” አላቸው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 28 \v 29 \v 30 28 ነገር ግን ምን ይመስላችኋል? አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት፣ ወደ መጀመሪያው ሄዶ፣’ልጄ፣ ዛሬ ወደ ወይኑ አትክልት ስፍራ ሄደህ ሥራ’ አለው። 29 ልጁ መልሶ፣ ‘አልሄድም’ አለ፤ በኋላ ግን ዐሳቡን ለውጦ ሄደ። 30 ሰውዬውም ወደ ሁለተኛው ልጅ ሄደ ይህንኑ ነገረው። ይህኛው ልጅ መልሶ፣ ‘እሄዳለሁ፣ አባዬ’ አለ። ነገር ግን አልሄድም።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 31 \v 32 31 ከዘለቁ ልጆች የአባቱን ትእዛዝ የፈጸመው የትኛው ነው? እነርሱ፣”የመጀመሪያው” አሉ። ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ “እውነት እላችኋለሁ፣ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና አመንዝራዎች ቀድመዋችሁ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባሉ። 32 ዮሐንስ በጽድቅ መንገድ ወደ እናንተ መጥቶ ነበርና፤ እናንተ ግን አላመናችሁትም፤ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና አመንዝራዎች ግን አመኑት። እናንተም ይህ ሲሆን አይታችሁ ታምኑት ዘንድ በኋላ እንኳ ንሰሐ አልገባችሁም።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 33 \v 34 3 ሌላም ምሳሌ ሰሙ። ሰፊ መሬት ያለው አንድ ሰው ነበር። የወይን አትክልት ተከለ፤ ዐጥር አጠረለት፤ የወይን መጥመቂያ ማሰለት፤ መጠበቂያ ማማ ሠራለት፤ ለወይን ገበሬዎችም አከራዩት ወደ ሌላ አገር ሄደ። 34 የወይን ፍሬ የሚሰበሰብበት ጊዜ እንደ ደረሰ፣ ፍሬውን እንዲቀበሉ ጥቂት አገልጋዮችን ላከ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 35 \v 36 \v 37 35 የወይኑ ገበሬዎች ግን አገልጋዮቹን ያዙ፤ አንዱን ደበደቡት፣ ሌላውን ገደሉት፤ ሌላውንም በድንጋይ ወገሩት። 36 ባለቤቱ እንደ ገና ከፊተኞቹ የበዙ ሌሎች አገልጋዮችን ላከ፤ ነገር ግን የወይን ገበሬዎቹ ያንኑ አደረጉባቸው። 37 ከዚያ በኋላ ባለቤቱ፣ ‘ልጄንስ ያከብሩታል’ በማለት የገዛ ልጁን ላከ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 38 \v 39 38 የወይን ገበሬዎቹ ግን ልጁን ባዩ ጊዜ፣ እርስ በርሳቸው፣’ይህ ወራሹ ነው፤ ኑ፣ እንግደለውና ርስቱን እንውረስ’ ተባባሉ። 39 ስለዚህ ያዙትና ከወይኑ የአትክልት ስፍራ ወደ ውጭ ጣሉት፤ ገደሉትም።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 40 \v 41 40 እንግዲህ የወይኑ አትክልት ባለቤት በሚመጣበት እነዚያን የወይን ገበሬዎች ምን ያደርጋቸዋል?” 41 ሕዝቡ እንዲህ አሉት፦ “እነዚያን ክፉ ሰዎች እጅግ በጣም አሰቃቂ በሆነ መንገድ ያጠፋቸዋል፤ ከዚያም የወይኑን አትክልት ስፍራ ወይኑ በሚያፈራበት ጊዜ ገንዘቡን ለሚከፍሉ ለሌሎች የወይን ገበሬዎች ያከራየዋል።”
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 42 42 ኢየሱስ እነርሱን፣ “ ‘ግንበኞች የናቁት ድንጋይ የማዕዘን ራስ ሆነ። ይህ ከጌታ ዘንድ ሆነ፤ለዐይኖቻችንም ድንቅ ነው ተብሎ የተጻፈውን ፈጽሞ አላነበባችሁም?’
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 43 \v 44 43 ስለዚህ እላችኋለሁ፣ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰድና ፍሬዋን ለሚያፈራ ሕዝብ ትሰጣለች። 44 በዚህ ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ሁሉ ይሰባበራል። ድንጋይ የሚወድቅበትን ሁሉ ግን ይፈጨዋል።”
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 45 \v 46 45 የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ምሳሌዎቹን በሰሙ ጊዜ፣ የተናገረው ስለ እነርሱ እንደሆነ ተረዱ። 46 ነገር ግን ሊይዙት በፈለጉ ጊዜ ሁሉ፣ ሰዎቹ እንደ ነቢይ ይቆጥሩት ስለ ነበር ሕዝቡን ፈሩ። a
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 23 \v 1 ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ሲል ተናገረ፤ \v 2 ‹‹የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል፡፡ \v 3 ስለዚህ የሚያዝዙዋችሁን ሁሉ አድርጉ፤ አክብሩትም፡፡ እነርሱ የሚያደርጉትን ግን አታደርጉ፤ ምክንያቱም እነርሱ ራሳቸው የሚናገሩትን አያደርጉትም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 4 ለመሸከም የሚያስቸግር ከባድ ሸክም አንሥተው ሰዎች ትከሻ ላይ ይጭናሉ፡፡ እነርሱ ራሳቸው ግን መሸከም ቀርቶ በጣታቸው ሊያነሡት እንኳ አይፈልጉም፡፡ \v 5 የሚያደርጉትን ሁሉ የሚያደርጉት በሰዎች ለመታየት ነው፤ አሸንክታባቸውን ያሰፋሉ፤ የልብሳቸውንም ዘርፍ ያስረዝማሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 6 ግብዣ ላይ የከበሬታ ቦታዎችንና በምኵራብ ውስጥ የተለየ መቀመጫ እንዲሰጣቸው ይፈልጋሉ፤ \v 7 በገበያ ቦታ ሰዎች የተለየ ክብር እንዲሰጧቸውና፣ ‹መምህር› በማለት እንዲጠሩዋቸው ይፈልጋሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 8 እናንተ ግን ያላችሁ አንድ መምህር ብቻ ስለሆነና ሁላችሁም ወንድማማች ስለሆናችሁ ‹መምህር› ተብላችሁ አትጠሩ፡፡ \v 9 በምድር ላይ ማንንም አባት ብላችሁ አትጥሩ፤ ምክንያቱም በሰማይ የሚኖር አንድ አባት ብቻ አላችሁ፡፡ \v 10 ‹ሊቅም› ተብላችሁ አትጠሩ፤ ምክንያቱም ያላችሁ አንድ ሊቅ ብቻ ነው፤ እርሱም ክርስቶስ ነው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 11 ከእናንተ መካከል ታላቅ የሆነው አገልጋያችሁ ይሁን፡፡ \v 12 ራሱን ከፍ የሚያደርግ ዝቅ ይላል፤ ራሱን ዝቅ የሚያደርግ ከፍ ይላል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 13 እናንት፣ ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ግን ወዮላችሁ! በሰዎች ፊት መንግሥተ ሰማይን ትዘጋላችሁ፡፡ እናንተ ራሳችሁ አትገቡበትም፤ የሚገቡትንም እንዳይገቡ ትከለክላላችሁ፡፡ 14 በጣም የታወቁ የጥንት ቅጂዎች ቁጥር 14 የላቸውም፡፡ (አንዳንድ ቅጂዎች ይህን እዚህና ከቁጥር 12 በኋላ አስገብተውታል)፡፡ \v 14 እናንት ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ለታይታ ረጅም ጸሎታችሁን በማድረግ የመበለቶችን ቤት ስለምትበሉ ወዮላችሁ! ስለዚህ የበለጠውን ፍርድ ትቀበላላችሁ፡፡ እናንተ ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! \v 15 አንድን ሰው ተከታያችሁ ለማድረግ በባሕርና በምድር ትሄዳላችሁ፤ ተከታያችሁ ካደረጋችሁት በኋላ፣ ከእናንተ ዕጥፍ የሚከፋ የገሃነም ልጅ ታደርጉታላችሁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 16 እናንት የታወራችሁ መሪዎች ወዮላችሁ፤ አንድ ሰው በቤተ መቅደሱ ቢምል ምንም ማለት አይደለም፤ ቤተ መቅደሱ ውስጥ ባለው ወርቅ ቢምል ግን፣ በመሐላው ይጠመዳል ትላላችሁ፡፡ \v 17 እናንት ደንቆሮ ዕውሮች፣ ለመሆኑ የትኛው ይበልጣል ወርቁ ወይስ ወርቁን የሚቀድሰው ቤተ መቅደሱ?
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 18 አንድ ሰው በመሠዊያው ቢምል ምንም ማለት አይደለም፤ መሠዊያው ላይ ባለው ስጦታ ቢምል ግን በመሐላው ይጠመዳል ትላላችሁ፡፡ \v 19 እናንት ዕውሮች፤ ለመሆኑ የትኛው ይበልጣል ስጦታው ወይስ ስጦታውን የሚቀድሰው መሠዊያ?
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 20 ስለዚህ በመሠዊያው የሚምል በመሠዊያውና እርሱ ላይ ባሉ ነገሮች ሁሉ ይምላል፡፡ \v 21 በቤተ መቅደሱ የሚምል በቤተ መቅደስና እርሱ ውስጥ በሚኖረው ይምላል፡፡ \v 22 በሰማይ የሚምል በእግዚአብሔር ዙፋንና እርሱ ላይ በተቀመጠው ይምላል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 23 እናንት ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ፣ ከአዝሙድ፣ ከእንስላልና ከከሙን ዐሥራት ብታወጡም፣ የሕጉን ዋና ዋና ነገሮች ማለትም ፍትሕን፣ ምሕረትንና እምነትን ሥራ ላይ አታውሉም፡፡ ሌላውን ችላ ሳትሉ እነዚህን መፈጸም ነበረባችሁ፡፡ \v 24 እናንት ዕውራን መሪዎች፣ ትንኝን አውጥታችሁ ትጥላላችሁ፤ ግመልን ግን ትውጣላችሁ!
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 25 እናንት ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! የጽዋውንና የወጪቱን ውጫዊ አካል ታጸዳላችሁ፤ ውስጡ ግን ቅሚያና ስስት ሞልቶበታል፡፡ \v 26 አንት ዕውር ፈሪሳዊ ውጫዊ አካሉም ንጹሕ እንዲሆን በመጀመሪያ የጽዋውንና የወጪቱን ውስጥ አጽዳ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 27 እናንት ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! ከውጭ ሲያዩት እንደሚያምር፣ ውስጡ ግን የሞቱ ሰዎች አጥንትና ርኵሰት እንደ ሞላበት መቃብር ናችሁ፡፡ \v 28 በተመሳሳይ መንገድ እናንተም ከውጭ ለሰዎች ጻድቅ ትመስላላችሁ፤ ውስጣችሁ ግን ግብዝነትና ርኩሰት ሞልቶበታል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 29 እናንት ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ የነቢያትን መቃብር ስለምትሠሩ፣ የጻድቃንን መቃብር ስለምታስጌጡ፣ \v 30 በአባቶቻችን ዘመን ኖረን ቢሆን ኖሮ፣ የነቢያትን ደም በማፍሰስ አንተባበራቸውም ነበር ትላላችሁ፡፡ \v 31 ስለሆነም የነቢያት ገዳይ ልጆች መሆናችሁን እናንተ ራሳችሁ ትመሰክራላችሁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 32 እናንተ ራሳችሁም አባቶቻችሁ የጀመሩትን ኃጢአት ትፈጽማላችሁ፡፡ \v 33 እናንት እባቦች፣ እናንት የእፉኝት ልጆች፣ ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ?
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 34 ስለዚህ ነቢያትን፣ አስተዋይ ሰዎችንና የአይሁድ ሕግ መምህራንን ወደ እናንተ እልካለሁ፡፡ አንዳንዶቹን ትገድላላችሁ፣ ትሰቅላላችሁ፤ ሌሎቹን በምኵራቦቻችሁ ትገርፋላችሁ፣ ከከተማ ወደ ከተማ ታሳድዳላችሁ፡፡ \v 35 ከጻድቁ አቤል አንሥቶ በቤተ መቅደሱና በመሠዊያው መካካል እስከ ገደላችሁት የበራክዩ ልጅ ዘካርያስ ደም ድረስ፣ በምድር ላይ በፈሰሰው ጻድቃን ደም ሁሉ ትጠየቃላችሁ፡፡ \v 36 እውነት ነው የሞላችሁ፤ እነዚህ ነገሮች ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይሆናሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 37 ኢየሩሳሌም፣ ኢየሩሳሌም ሆይ አንቺ ነቢያትን የምትገድዪ ወደ አንቺ የተላኩትን በድንጋይ የምትወግሪ! ዶሮ ጫጩቶችዋን በክንፎቿ ሥር እንደምትሰበስብ እኔም ልጆችሽን መሰብሰበ ብዙ ጊዜ ፈልጌ ነበር፤ እናንተ ግን አልፈለጋችሁም! \v 38 ስለሆነም ቤታችሁ ወና ሆኖ ይቀራል፡፡ \v 39 ‹‹በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው›› እስክትሉ ድረስ ከአሁን ጀምሮ አታዩኝም እላችኋለሁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 24 \v 1 ኢየሱስ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ እየሄደ ሳለ፤ ደቀ መዛሙርቱ የቤተ መቅደሱን ሕንፃ ሊያሳዩት ወደ እርሱ መጡ፡፡ \v 2 እርሱ ግን፣ ‹‹እነዚህን ሁሉ ነገሮች ታያላችሁ? እውነት ነው የምላችሁ፤ ይፈርሳል እንጂ፣ አንዲት ድንጋይ እንኳ በሌላ ድንጋይ ላይ እንደ ተነባበረ አይቀርም›› በማለት መለሰላቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 3 ደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ እያለ፣ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ መጥተው፣ ‹‹እስቲ ንገረን፤ ይህ ሁሉ የሚሆነው መቼ ነው? የአንተ መምጣትና የዓለም መጨረሻስ ምልክቱ ምንድን ነው?›› አሉት፡፡ \v 4 ኢየሱስም መልሶ፣ ‹‹ማንም እንዳያሳስታችሁ ተጠንቀቁ፡፡ \v 5 ምክንያቱም ብዙዎች በስሜ ይመጣሉ፤ ‹እኔ ክርስቶስ ነኝ› እያሉ ብዙዎችን ያሳስታሉ›› አላቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 6 ጦርነትንና የጦርነት ዜና ትሰማላችሁ፤ በፍጹም እንዳትታወኩ፤ ምክንያቱም እነዚህ ነገሮች እንዲሆኑ ግድ ነው፤ ቢሆንም፣ መጨረሻው ገና ነው፡፡ \v 7 ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥት በመንግሥት ላይ ይነሣል፡፡ በተለያየ ቦታ ችጋርና የምድር መናወጥ ይሆናል፡፡ \v 8 እነዚሀ ሁሉ ግን የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 9 ከዚያም ለመከራ አሳልፈው ይሰጧችኋል ደግሞም ይገድሏችኋል፡፡ ስለ ስሜ በሕዝቦች ሁሉ ትጠላላችሁ፡፡ \v 10 ብዙዎች ይሰነካከላሉ፤ እርስ በርስ ይካካዳሉ፤ እርስ በርስ ይጠላላሉ፡፡ \v 11 ብዙ ሐሰተኛ ነቢያት ተነሥተው፣ ብዙዎችን ያሳስታሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 12 ዐመፅ ስለሚበዛ የብዙዎች ፍቅር ይቀዘቅዛል፡፡ \v 13 እስከ መጨረሻ የሚታገሥ ግን ይድናል፡፡ \v 14 ለሕዝቦች ሁሉ ምስክር እንዲሆን የመንግሥቱ ወንጌል ለመላው ዓለም ይሰበካል፤ ከዚያ መጨረሻው ይመጣሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 15 15 ስለዚህ በነቢዩ ዳንኤል የተነገረለት የጥፋት ርኩሰት በተተቀደሰው ቦታ ቆሞ ስታዩ፣ (ያኔ አንባቢው ያስተውል) 16 \v 16 በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፣ 17 \v 17 በጣርያ ላይ ያለ ሰው ቤቱ ያለውን ምንም ነገር ከቤቱ ለመውሰድ አይመለስ፣ \v 18 18 በእርሻ ያለ ልብሱን ለመውሰድ አይመለስ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 19 ልጆች ላሉዋቸውና ለሚያጠቡ እናቶች ግን ወዮላቸው! \v 20 ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፡፡ \v 21 ምክንያቱም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስና ከዚያም በኋላ ፈጽሞ የማይሆን ታላቅ መከራ ይሆናል፡፡ \v 22 እነዚያ ቀኖች ባያጥሩ ኖሮ፣ ማንም ሥጋ ለባሽ አይድንም ነበር፤ ለተመረጡት ሲባል ግን እነዚያ ቀኖች ያጥራሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 23 ስለዚህ ማንም ‹‹ክርስቶስ እዚህ ነው›› ቢላችሁ ወይም፣ ‹‹ክርስቶስ እዚያ ነው›› ቢላችሁ አትመኑ፡፡ \v 24 ምክንያቱም ብዙዎችን ለማሳሳት ሐሰተኛ ክርስቶሶችና ሐሰተኛ ነቢያት መጥተው ታላላቅ ምልክቶችና ድንቆችን ያደርጋሉ፤ ከተቻለም የተመረጡትን እንኳ ያሳስታሉ፡፡ \v 25 ይህ ከመሆኑ በፊት አስቀድሜ ነግሬአችኋለሁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 26 ስለዚህ፣ ‹ክርስቶስ በምድረ በዳ ነው› ቢሏችሁ ወደ ምድረ በዳ አትሂዱ ወይም ቤት ውስጥ ነው ቢሏችሁ አትመኑ፡፡ \v 27 መብረቅ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ በአንዴ እንደሚታይ የሰው ልጅ ሲመጣ እንደዚያው ይሆናል፡፡ \v 28 የሞተ እንስሳ ባለበት ሁሉ፣ በዚያ አሞሮች ይሰበሰባሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 29 29 ከእነዚህ የመከራ ቀኖች በኋላ ወዲያውኑ ፀሐይ ትጨልማለች፣ ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም፤ ከዋክብት ከሰማይ ይወድቃሉ፤ የሰማያት ኃይሎች ይናወጣሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 30 ከዚያም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፤ የምድር ነገዶች ሁሉ አምርረው ያለቅሳሉ፡፡ የሰው ልጅንም በኀይልና በታላቅ ክብር ሲመጣ ያዩታል፡፡ \v 31 መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፤ እነርሱም፣ ከአንድ የሰማይ ጫፍ እስከ ሌላው ጫፍ ድረስ ከአራቱም ማእዘኖች ምርጦቹን ይሰበስቧቸዋል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 32 ከበለስ ዛፍ ተማሩ፡፡ ቅርንጫፎቹ ሲለመልሙና ቅጠሎች ብቅ ብቅ ሲሉ በጋ መቅረቡን ታውቃላችሁ፡፡ \v 33 እናንተም እነዚህን ሁሉ ስታዩ እርሱ መቅረቡን፣ እንዲያውም በደጅ መሆኑን ዕወቁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 34 እውነት ነው የምላችሁ፤ እነዚህ ሁሉ እስኪፈጸሙ ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም፡፡ \v 35 ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን ፈጽሞ አያልፍም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 36 36 ስለዚያች ቀንና ሰዓት ግን ማንም አያውቅም፤ የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ አያወቁም፤ አብ ብቻ እንጂ ወልድ እንኳ ቢሆን አያውቅም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 37 በኖኅ ዘመን እንደ ነበረው፣ የሰው ልጅ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል፡፡ \v 38 ከጥፋት ውሃ በፊት እንደ ነበረው ዘመን፣ ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባ ድረስ ይበሉና ይጠጡ፣ ያገቡና ይጋቡ ነበር \v 39 ጐርፉ መጥቶ እስኪያጠፋቸው ድረስ ምንም አላወቁም፣ የሰው ልጅ ሲመጣም እንዲሁ ይሆናል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 40 በዚያን ጊዜ ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሌላው ይቀራል፡፡ \v 41 ሁለት ሴቶች በወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዷ ትወሰዳለች አንዷ ትቀራለች፡፡ \v 42 ስለዚህ ጌታችሁ በምን ቀን እንደሚመጣ አታውቁምና ተጠንቀቁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 43 ይህን ግን ዕወቁ፤ ሌባው በየትኛው ሰዓት እንደሚመጣ የቤቱ ባለቤት ቢያውቅ ኖሮ ይጠነቀቅ ነበር፤ ቤቱ አይዘረፍም ነበር፡፡ \v 44 የሰው ልጅ ባልጠበቃችሁት ሰዓት ስለሚመጣ እናንተም ብትሆኑ ተዘጋጅታችሁ መጠበቅ አለባችሁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 45 በተገቢው ጊዜ ለቤተ ሰቡ ምግባቸውን ለመስጠት ጌታው በቤቱ ላይ ኀላፊነት የሰጠው ታማኝና አስተዋይ አገልጋይ ማነው? \v 46 ጌታው ሲመጣ ያንን እያደረገ የሚያገኘው አገልጋይ የተባረከ ነው፡፡ \v 47 እውነቴን ነው የምላችሁ፣ ጌታው ባለው ነገር ሁሉ ላይ ኀላፊ አድርጐ ይሾመዋል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 48 \v 49 \v 50 48 ይሁን እንጂ፣ አንድ ክፉ አገልጋይ በልቡ፣ ‹‹ጌታዬ ከመምጣት ዘግይቶአል ብሎ ቢያስብ፣ 49 አገልጋይ ጓደኞቹን መደብደብና ከሰካራሞች ጋር መብላት መጠጣት ቢጀምር 50 የዚያ አገልጋይ ጌታ አገልጋዩ ባልጠበቀው ቀንና በማያውቀው ሰዓት ይመጣበታል፡፡ 51 \v 51 ጌታው ለሁለት ይሰነጥቀዋል፤ ዕጣ ፈንታውን ከግብዞች ጋር ያደርግበታል፣ በዚያም ለቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 25 \v 1 መንግሥተ ሰማይ መብራታቸውን ይዘው ሙሽራውን ለመቀበል የወጡ ዐሥር ድንግል ሴቶችን ትመስላለች። \v 2 አምስቱ ሞኞች፣ አምስቱ ልባሞች ነበሩ። \v 3 ሞኞቹ ሴቶች መብራታቸውን ይዘው ሴሄዱ ምንም ዘይት አልያዙም ነበር። \v 4 ልባሞቹ ግን ከመብራታቸው ጋር ዘይትም ይዘው ነበር።
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 5 ሙሽራው በዘገዬ ጊዜ እንቅልፍ እንቅልፍ አላቸውና ሁሉም ተኙ።
|
||||
\v 6 ዕኩለ ሌሊት ላይ ግን፣ “ሙሽራው መጥቶአልና ወጥታችሁ ተቀበሉት!” የሚል ሁካታ ሆነ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 7 ያኔ እነዚያ ድንግሎች ሁሉ ተነሥተው መብራታቸውን አዘጋጁ። \v 8 ሞኞቹም ልባሞቹን፣ “መብራታችን እየጠፋ ስለሆነ ከዘይታችሁ ጥቂት ስጡን” አሏቸው። \v 9 ልባሞቹ ግን፣ “ለእኛና ለእናንተ የሚበቃ ስለሌለን፣ ወደ ሻጮች ሄዳችሁ ለራሳችሁ ግዙ” በማለት መለሱአቸው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 10 ለመግዛት ሲሄዱ፣ ሙሽራው መጣ፤ ተዘጋጅተው የነበሩት ግብዣው ላይ ለመገኘት ከእርሱ ጋር ሄዱ፤ በሩም ተዘጋ። \v 11 በኋላም ሌሎቹም ድንግሎች መጥተው፣ “ጌታው፣ በሩን ክፈትልን” አሉ። \v 12 እርሱ ግን መልሶ፣ “በእውነት ነው የምላችሁ አላውቃችሁም” አላቸው። \v 13 ስለዚህ ቀኑን ወይም ሰዓቱን አታውቁምና ነቅታችሁ ጠብቁ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 14 ነገሩ ወደ ሌላ አገር መሄድ ያሰበ ሰውን ይመስላል፤ አገልጋዮቹን ጠርቶ በሀብት በንብረቱ ሁሉ ላይ ኀላፊነት ሰጣቸው። \v 15 እንደ ዐቅማቸው መጠን ለአንዱ አምስት ታላንት፣ ለሌላው ሁለት፣ ለሌላው ደግሞ አንድ ታላንት ሰጣቸውና ሄደ። \v 16 አምስት ታላንት የተቀበለው ወዲያውኑ ሄዶ ነገደበት፤ ሌላ አምስት አተረፈ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 17 ሁለት ታላንት የተቀበለውም እንደዚያው ሌላ ሁለት ታላንት አተረፈ። \v 18 አንድ ታላንት የተቀበለው አገልጋይ ግን ሄዶ፣ ጉድጓድ ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 19 ከብዙ ጊዜ በኋላ የእነዚያ አገልጋዮች ጌታ ተመልሶ መጣና ተሳሰበቸው።
|
||||
\v 20 አምስት ታላንት የተቀበለው አገልጋይ ሌላ አምስት ታላንት ጨምሮ አመጣና፣ “ጌታው አምስት ታላንት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እኔ ግን ሌላ አምስት ታላንት አተረፍሁ” አለ። \v 21 ጌታውም፣ “አንተ መልካምና ታማኝ አገልጋይ ደግ አደረግህ! በጥቂት ነገሮች ታምነሃል፤ በብዙ ነገሮች ላይ እሾምሃለሁ። ወደ ጌታህ ደስታ ግባ።” አለው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 22 ሁለት ታላንት ተቀብሎ የነበረው አገልጋይም መጥቶ፣ ‘ጌታው፣ ሁለት ታላንት ሰጥተኸኝ ነበር። ሌላ ሁለት ታላንት አትርፌአለሁ’ አለ። \v 23 ጌታውም፣ “አንተ መልካምና ታማኝ አገልጋይ ደግ አደረግህ! በጥቂት ነገሮች ታምነሃል፤ በብዙ ነገሮች ላይ እሾምሃለሁ። ወደ ጌታህ ደስታ ግባ’ አለው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 24 ከዚያም አንድ ታላንት የተቀበለው አገልጋይ መጥቶ፣ “ጌታው፣ ካልዘራህበት የምታጭድ፣ ካልበተንህበት የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ። \v 25 ስለዚህ ፈራሁ፤ ታላንትህን መሬት ውስጥ ቀበርሁት። ታላንትህ ይኸውልህ አለው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 26 ጌታው ግን መልሶ፣ “አንተ ዐምፀኛና ሰነፍ አገልጋይ፤ ካልዘራሁበት የማጭድ፣ ካልበተንሁበት የምሰበስብ መሆኔን ታውቃለህ። \v 27 ስለዚህ ገንዘቤን ለአትራፊዎች መስጠት ይገባህ ነበር፤ እኔ ስመጣ ከእነ ትርፉ እወስደው ነበር” አለው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 28 ስለዚህ ታላንቱን ከእርሱ ወስዳችሁ ዐሥር ታላንት ላለው ስጡት። \v 29 ላለው የበለጠ እንዲያውም የተትረፈረፈ ይሰጠዋል። ምንም ከሌለው ግን፣ ያው ያለው ነገር እንኳ ይወሰድበታል። \v 30 ይህን የማይረባ አገልጋይ አውጡና ለቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት በውጭ ወዳለው ጨለማ ጣሉት” አለ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 31 የሰው ልጅ በክብሩ ከመላእክቱ ሁሉ ጋር ሲመጣ፣ በክብር ዙፋኑ ላይ ይቀመጣል። \v 32 አሕዛብ ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛ በጎችን ከፍየሎች እንደሚለይ ሕዝቡን ይለያቸዋል። \v 33 በጐቹን በቀኙ፣ ፍየሎቹን በግራው ያደርጋቸዋል።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 34 ከዚያም ንጉሡ በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፤ “እናንት አባቴ የባረካችሁ ኑ፤ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት ያዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። \v 35 ተርቤ ነበር ምግብ ሰጣችሁኝ፤ ተጠምቼ ነበር የምጠጣው ሰጣችሁኝ፤ እንግዳ ሆኜ ነበር አስተናገዳችሁኝ፤ \v 36 ተራቁቼ ነበር አለበሳችሁኝ፤ ታምሜ ነበር ተንከባከባችሁኝ፤ ታስሬ ነበር ጠየቃችሁኝ” ይላቸዋል።
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 37 ጻድቃንም እንዲህ ይመልሱለታል፣ ‘ጌታው፣ ተርበህ ያገኘንህና ያበላንህ ወይስ ተጠምተህ ያጠጣንህ መቼ ነው? \v 38 38 እንግዳ ሆነህ ያየንህና ያስተናገድንህ መቼ ነው? ወይም ተራቁተህ ያለበስንህ መቼ ነው? \v 39 ታምመህ የተንከባከብንህ ወይስ ታስረህ የጠየቅንህ መቼ ነው?’
|
||||
\v 40 ንጉሡም መልሶ እንዲህ ይላቸዋል ‘እውነት ነው የምላችሁ፤ ለእነዚህ ታናናሽ ወንድሞቼ ያደረጋችሁትን ለእኔ አድርጋችሁታል።’
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 41 ከዚያም በግራው ያሉትን፣ ‘እናንተ ርጉማን ከእኔ ራቁ፤ ለዲያብሎስና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀው ገሃነም እሳት ሂዱ። \v 42 ምክንያቱም ‘ተርቤ ነበር አላበላችሁኝም፤ ተጠምቼ ነበር አላጠጣችሁኝም፤ \v 43 እንግዳ ሆኜ ነበር አላስተናገዳችሁኝም፤ ተራቁቼ ነበር አላለበሳችሁኝም፤ ታምሜ፣ ታስሬ ነበር አልተንከባከባችሁኝም’ ይላቸዋል።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 44 እነርሱም መልሰው እንዲህ ይሉታል፤ ‘ጌታ፣ ተረበህ ወይም ተጠምተህ ወይም እንግዳ ሆነህ ወይም ተራቁተህ ወይም ታምመህ ወይም ታስረህ ያላገለገልንህ መቼ ነው?’ \v 45 እርሱም መልሶ፣ ‘እውነት ነው የምላችሁ ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ አለማድረጋችሁ ለእኔ አለማድረጋችሁ ነው’ ያላቸዋል። \v 46 እነዚህ ወደ ዘላለም ቅጣት፣ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 26 \v 1 ኢየሱስ እነዚህን ተናግሮ እንደ ጨረሰ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፤ \v 2 ‹‹ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንደሚሆን ታውቃላችሁ፣ የሰው ልጅም ተሰቅሎ እንዲገደል ተላልፎ ይሰጣል፡፡››
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 3 ከዚያ የካህናት አለቆቹና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ቀያፋ በሚሉት ሊቀ ካህን ቤተ መንግሥት ውስጥ ተሰበሰቡ፤ \v 4 ኢየሱስን በረቀቀ ዘዴ ለማሰርና ለመግደል ተማከሩ፡፡ \v 5 ምክንያቱም፣ በሕዝቡ መሓል ረብሻ እንዳይነሣ በበዓሉ ሰሞን መሆን የለበትም እያሉ ነበር፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 6 ኢየሱስ በቢታንያ በለምጻሙ ስምዖን ቤት \v 7 ማዕድ ላይ ተቀምጦ እያለ፣ አንዲት ሴት ዋጋው ውድ የሆነ የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ መጣችና ራሱ ላይ አፈሰሰች፡፡ \v 8 ደቀ መዛሙርቱ ይህን ሲያዩ በጣም ተቆጥተው፣ ‹‹ይህ ብክነት ምንድን ነው? \v 9 ይህ እኮ ከፍ ባለ ዋጋ ተሸጦ ገንዘቡን ለድኾች መስጠት ይቻል ነበር አሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 10 ኢየሱስም ይህን ዐወቆ እንዲህ አላቸው፣ ‹‹ይህችን ሴት ለምን ታስቸግሯታላችሁ? ለእኔ መልካም ነገር አድርጋለች፡፡ \v 11 ድኾች ሁሌም ከእናንተ ጋር ናቸው፤ እኔ ግን ሁሌ ከእናንተ ጋር አልሆንም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 12 ይህን ሽቶ እኔ ላይ ያፈሰሰች ጊዜ ለቀብሬ አድርጋዋለች፡፡ \v 13 እውነት ነው የምላችሁ ይህ ወንጌል በመላው ዓለም ሲሰበክ ለእርሷ መታሰቢያ እንዲሆን ይህች ሴት ያደረገችውም ይነገርላታል›› አላቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 14 ከዚያም የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆቹ ሄዶ፣ \v 15 ‹‹እርሱን አሳልፌ ብሰጣችሁ ለእኔ ምን ትሰጡኛላችሁ?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ሰላሣ ጥሬ ብር ተመኑለት፡፡ \v 16 ከዚያ ጊዜ ወዲህ እርሱን አሳልፎ የሚሰጥበትን ምቹ ጊዜ ይጠባበቅ ጀመር፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 17 ቂጣ በሚበላበት መጀመሪያ ግን ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ መጥተው፣ ‹‹የፋሲካን እራት እንድትበላ የት እንድናዘጋጅልህ ትፈልጋለህ?›› አሉት፡፡ \v 18 እርሱም፣ ‹‹ከተማው ውስጥ ወዳለ አንድ ሰው ሂዱና ‹መምህሩ ‹‹ጊዜዬ ደርሷል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን አንተ ቤት ማሳለፍ እፈልጋለሁ› ይልሃል በሉት አላቸው፡፡ \v 19 ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ እንደ ነገራቸው አደረጉ፤ የፋሲካንም እራት አዘጋጁለት፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 20 ምሽት ላይ ከዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ጋር ለመብላት ተቀመጠ፡፡ \v 21 በመብላት ላይ እያሉ፣ ‹‹እውነት ነው የምላችሁ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል›› አላቸው፡፡ \v 22 በጣም አዘኑ፤ እያንዳንዱም፣ ‹‹እኔ እሆን?›› በማለት ጠየቀ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 23 እርሱም፣ ‹‹አሳልፎ የሚሰጠኝ ከእኔ ጋር እጁን ወደ ሳህኑ የሚሰደው ነው፡፡ \v 24 የሰው ልጅ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈው ይሄዳል፤ የሰውን ልጅ አሳልፎ ለሚሰጠው ግን ወዮለት! ያ ሰው ባይወለድ ይሻለው ነበር›› በማለት መለሰላቸው፡፡ \v 25 አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳ፣ ‹‹መምህር እኔ ነኝ እንዴ? አለው፤ እርሱም፣ ‹‹አንተው ራስህ ብለኸዋል›› አለው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 26 በመብላት ላይ እያሉ፣ ኢየሱስ እንጀራ አንሥቶ ባርኮ ቆረሰ፡፡ ‹‹እንካችሁ ውሰዱ፣ ብሉት፤ ይህ ሥጋዬ ነው›› ብሎ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 27 ጽዋውንም አንሥቶ አመሰገነና ሰጣቸው፤ እንዲህም አላቸው፣ ‹‹ሁላችሁም ጠጡት \v 28 ይህ ለብዙዎች ኀጢአት ይቅርታ የሚፈስ የኪዳኑ ደሜ ነው፡፡ \v 29 እንደ ገና በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር እስክጠጣው ድረስ ከእንግዲህ ከዚህ ወይን ፍሬ እንደማልጠጣ ግን እነግራችኋለሁ፡፡››
|
|
@ -0,0 +1,3 @@
|
|||
\v 30 መዝሙር ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ወጡ፡፡ \v 31 ያኔ ኢየሱስ፣ ‹‹በዚህ ሌሊት ሁላችሁም በእኔ ምክንያት ትሰናከላላችሁ፤ ምክንያቱም፣
|
||||
‹‹እረኛውን እመታለሁ
|
||||
በጎቹም ይበተናሉ›› ተብሎ ተጽፎአል፡፡ \v 32 ከተነሣሁ በኋላ ግን ቀድሜአችሁ ወደ ገሊላ እሄዳለሁ›› አላቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 33 ጴጥሮስ ግን፣ ‹‹ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እንኳ እኔ አልሰናከልም›› አለው፡፡ \v 34 ኢየሱስም፣ ‹‹እውነት ነው የምልህ፣ በዚህች ሌሊት ዶሮ ከመጮኹ በፊት ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ›› አለው፡፡ \v 35 ጴጥሮስም፣ ‹‹ከአንተ ጋር መሞት ቢኖርብኝ እንኳ አልክድህም›› አለ፡፡ ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ሁሉ እንደዚያው አሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 36 ከዚያም ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደሚሉት ቦታ ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱንም፣ ‹‹ወደዚያ ሄጄ እስክጸልይ ድረስ እዚህ ሁኑ›› አላቸው፡፡ \v 37 ጴጥሮስንና ሁለቱን የዘብዴዎስ ልጆች ይዞ ሄደ፤ ያዝንና ይጨነቅም ጀመር፡፡\v \v 38 ከዚያም፣ ‹‹ነፍሴ፣ እስከ ሞት ድረስ በጣም አዝናለች፡፡ እዚህ ሆናችሁ ከእኔ ጋር ትጉ›› አላቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 39 ጥቂት ራቅ ብሎ በመሄድ በግንባሩ ወድቆ ጸለየ፤ ‹‹አባት ሆይ፣ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ፤ ይሁን እንጂ፣ የእኔ ፈቃድ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን›› አለ፡፡ \v 40 ወደ ደቀ መዛሙርቱ ሲመጣ ተኝተው አገኛቸው፤ ጴጥሮስንም፣ ‹‹ከእኔ ጋር አንድ ሰዓት ያህል እንኳ መትጋት አልቻልህምን? \v 41 ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፡፡ መንፈስ በእርግጥ ፈቃደኛ ነው፤ ሥጋ ግን ደካማ ነው›› አለው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 42 ለሁለተኛ ጊዜ ጥቂት ፈቀቅ ብሎ ጸለየ፤ ‹‹አባት ሆይ፣ እኔ ካልጠጣሁት በቀር ይህ የማያልፍ ከሆነ፣ ፈቃድህ ይሁን›› አለ፡፡ \v 43 እንደ ገና ሲመጣ ዐይኖቻቸው ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው፡፡ \v 44 እንደ ገና ትቶአቸው ሄዶ ለሦስተኛ ጊዜ ያንኑ ቃል ጸለየ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 45 ከዚያም ኢየሱስ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጥቶ፣ ‹‹አሁንም ዐርፋችሁ ተኝታችኋል? ጊዜው ደርሷል፤ የሰው ልጅ በኀጢአተኞች እጅ ተላልፎ ይሰጣል፡፡ \v 46 እንግዲህ ተነሡ እንሂድ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቧል›› አላቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 47 ገና እየተናገረ እያለ፣ ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነው ይሁዳ መጣ፣ ከእርሱም ጋር ከካህናት አለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሌዎች የመጡ ሰይፍና ዱላ የያዙ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ \v 48 በዚህ ጊዜ አሳልፎ የሚሰጠው፣ ‹‹እኔ የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት›› የሚል ምልክት ሰጣቸው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 49 ወዲያውኑ ወደ ኢየሱስ መጥቶ፣ ‹‹መምህር፣ ሰላም ለአንተ ይሁን!›› ብሎ ሳመው፡፡ \v 50 ኢየሱስም፣ ‹‹ወዳጄ፣ የመጣህበትን ጉዳይ ፈጽም›› አለው፡፡ ከዚያም ቀርበው ኢየሱስን ያዙት አሰሩት፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 51 ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ እጁን ዘርግቶ ሰይፍ አወጣ፤ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮ መትቶ ቆረጠ፡፡ \v 52 ያኔ ኢየሱስ፣ ‹‹ሰይፍህን ወደ ቦታው መልስ፤ ሰይፍ የሚያነሡ በሰይፍ ይጠፋሉ፡፡ \v 53 አባቴን ብጠይቅ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ መላእክት የማይልክልኝ ይመስልሃል? \v 54 እንደዚያ ከሆነ ይህ እንደሚሆን የሚናገረው መጽሐፉ ቃል እንዴት ይፈጸማል?›› አለው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 55 \v 56 55 በዚያ ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡ፣ ‹‹አንድ ወንበዴ እንደምትይዙ ሰይፍና ዱላ ይዛችሁ መጣችሁ? በየቀኑ በቤተ መቅደስ ተቀምጬ እያስተማርሁ ነበርሁ፡፡ እናንተም አልያዛችሁኝም ነበር፡፡ 56 የነቢያት መጽሐፍ እንዲፈጸም ይህ ሆኗል›› አላቸው፡፡ ያኔ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ትተውት ሸሹ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 57 ኢየሱስን የያዙ ሰዎች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ሽማግሌዎቹ ተሰብስበው ወደ ነበሩበት ወደ ሊቀ ካህኑ ወደ ቀያፋ ቤት ወሰዱት፡፡ \v 58 ጴጥሮስ ግን ከሩቅ ሆኖ እስከ ሊቀ ካህኑ ግቢ ድረስ ተከተለው፤ ወደ ውስጥ ገብቶም የሚሆነውን ለማየት ከጠባቂዎቹ ጋር ተቀመጠ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 59 እርሱን ለማስገደል የካህናት አለቆቹና ሸንጐው ሁሉ ኢየሱስ ላይ በሐሰት የሚመሰክሩበት ሰዎች እየፈለጉ ነበር፡፡ \v 60 ምንም እንኳ ብዙ የሐሰት ምስክሮች ቢመጡም፤ በቂ ማስረጃ አላገኙም፡፡ በኋላ ግን ሁለት ሰዎች መጥተው፣ \v 61 ‹‹ይህ ሰው፣ ‹የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ በሦስት ቀን ውስጥ እንደ ገና ልሠራው እችላለሁ›› ብሏል አሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 62 ሊቀ ካህናቱ ተነሥቶ፣ ‹‹መልስ የለህም? እየመሰከሩብህ ያለው ምንድን ነው?›› አለው፡፡ \v 63 ኢየሱስ ግን ዝም አለ፡፡ ሊቀ ካህናቱም፣ ‹‹በሕያው እግዚአብሔር አዝሃለሁ፤ አንተ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን አለመሆንህን ንገረን›› አለው፡፡ \v 64 ኢየሱስም፣ ‹‹አንተው ራስህ አልህ፤ ግን ልንገርህ፣ ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በኀይል ቀኝ በሰማይ ደመና ሲመጣ ታያለህ›› በማለት መለሰለት፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 65 ያኔ ሊቀ ካህናቱ ልብሱን ቀደደና፣ ‹‹እግዚአብሔርን ተሳድቧል፤ ታዲያ፣ ምስክር የምንፈልገው ለምንድን ነው? አሁን ስድቡን ሰምታችኋል \v 66 ለመሆኑ፣ ምን ታስባላችሁ?›› አለ፡፡ እነርሱም መልሰው ‹‹ሞት ይገባዋል›› አሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 67 ያኔ ፊቱ ላይ ተፉበት፣ በጡጫና በጥፊ መቱት፤ \v 68 ‹‹አንተ ክርስቶስ እስቲ ትንቢት ተናገር፡፡ ለመሆኑ፣ በጥፊ የመታህ ማነው?›› አሉት፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 69 በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ እደጅ ግቢው ውስጥ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት አገልጋይ ልጅ ወደ እርሱ መጥታ፣ ‹‹አንተም ደግሞ ከገሊላው ኢየሱስ ጋር ነበርህ›› አለችው፡፡ \v 70 እርሱ ግን፣ ‹‹ምን እየተናገርሽ እንደ ሆነ አላውቅም›› በማለት በሁሉም ፊት ካደ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 71 ከግቢው ወደሚያስወጣው በር እየሄደ እያለ፣ ሌላ አገልጋይ ልጅ አየችውና እዚያ ለነበሩት፣ ‹‹ይህኛውም ሰውየ ከናዝሬቱ ኢየሱስ ጋር ነበረ›› አለች፡፡ \v 72 እርሱም፣ ‹‹ሰውየውን አላውቀወም›› በማለት በመሐላ ጭምር በድጋሚ ካደ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 73 ጥቂት ቆየት ብሎ እዚያ ቆመው የነበሩት መጥተው ጴጥሮስን፣ ‹‹በእርግጥ አንተም ብትሆን ከእነርሱ አንዱ ነህ፤ አነጋገርህ ራሱ ያጋልጥሃል›› አሉት፡፡ \v 74 ያኔ፣ ‹‹ሰውየውን ጨርሶ አላውቀውም›› በማለት ይራገምና ይምል ጀመር፤ ወዲያውኑ ዶሮ ጮኸ፡፡ \v 75 ጴ¬ጥሮስ ‹‹ዶሮ ሳይጮኽ ሦስቴ ትክደኛለህ›› በማለት ኢየሱስ የተናገረውን አስታወሰ፡፡ ከዚያ ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 27 \v 2 \v 1 ጠዋት በማለዳ የካህናት አለቆቹና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ሁሉ ኢየሱስን ለመግደል ተማከሩ።\v 2 አስረው ወሰዱትና ለአገሩ ገዡ ጲላጦስ አስረከቡት።
|
Some files were not shown because too many files have changed in this diff Show More
Loading…
Reference in New Issue