\c 3 \v 1 ጢባርዮስ ቄሣር በነገሠ በአሥራ አምስተኛው ዓመት፣ ጴንጤናዊው ጲላጦስ የይሁዳ ገዥ፣
ሄሮድስ የገሊላ አራተኛው ክፍል ገዥ፣ ወንድሙ ፊልጶስ የኢጡርያስና የጥራኮኒዶስ የአራተኛው ክፍል ገዥ፣ ሊሳኒዮስም የሳቢላኒስ አራተኛው ክፈል ገዥ \v 2 እንደዚሁም ሐናና ቀያፋ ሊቃነ ካህናት በነበሩበት ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል ለዘካርያስ ልጅ ለዮሐንስ በምድረ-በዳ መጣ፡፡