\v 16 እግዚአብሔር ከማደሪያው በትኖአቸዋል፥ ከእንግዲህ ወድያ ወደ እነርሱ በርኅራኄ አይመለከትም። ማንም ከእንግዲህ ወድያ ካህናቱን በምንም መልኩ አክብሮ አይቀበላቸውም፥ ለሽማግሌዎቹም ግድ አልተሰኙም።