Mon Jun 19 2017 14:37:46 GMT+0300 (E. Africa Standard Time)
This commit is contained in:
parent
ecbee0fd34
commit
0a0bce150a
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 8 \v 9 8 ብርና ወርቁ የእኔ ነው! ይህ የሠራዊት ጌታ የያህዌ ዐዋጅ ነው።
|
||||
9 የወደፊቱ የዚህ ቤት ክብር ከመጀመሪያው ይበልጣል ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ፤ በዚህ ቦታ ሰላም እሰጣለሁ - ይህ የሠራዊት ጌታ የያህዌ ዐዋጅ ነው።”
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 10 \v 11 \v 12 10 ዳርዮስ በነገሠ ሁለተኛው ዓመት፣ በዘጠነኛው ወር ሃያ አራተኛ ቀን የያህዌ ቃል በነቢዩ በሐጌ በኩል መጣ፤ እንዲህም አለ፣ 11 “የሠራዊት ጌታ ያህዌ እንዲህ ይላል፤ ሕጉ ምን እንደሚል ካህናቱን ጠይቁ፤ አንድ ሰው ለያህዌ የተቀደሰውን ሥጋ በልብሱ እጥፋት ቢይዝ፣ በልብሱ እጥፋት እንጀራ ወይም ወጥ፣ የወይን ጠጅ ወይም ዘይት ወይ ሌላ ምግብ ቢነካ፣ ያ ምግብ ይቀደሳልን?” ካህናቱም፣ “የለም፣ አይቀደስም” በማለት መለሱ።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 13 \v 14 13 ሐጌም፣ “ሬሳ በመንካቱ የረከሰ ሰው ከእነዚህ አንዱን ቢነካ ይረክሳሉን?” አለ። ካህናቱም፣ “አዎን፣ ይረክሳሉ” በማለት መለሱ። 14 ስለዚህ ሐጌ መልሶ፣ “ ይህም ሕዝብ በፊቴ እንዲሁ ነው!- ይህ የያህዌ ዐዋጅ ነው፤ የእጃቸው ሥራና ለእኔ የሚያቀርቡት ሁሉ የረከሰ ነው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 15 \v 16 \v 17 15 እንግዲህ ከዘሬ ጀምራችሁ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ከመነባበሩ በፊት የነበረውን ሁኔታ ልብ በሉ፤ 16 ለምሆኑ ያኔ እንዴት ነበር? አንድ ሰው ሃያ መስፈሪያ እህል ጠብቆ ወደ ክምሩ ሲሄድ አሥር ብቻ አገኘ። አምሳ ማድጋ ወይን ጠጅ ለመቅዳት ወደ መጭመቂያው ሲሄድ ሃያ ብቻ አገኘ። 17 እናንተንና የእጆቻችሁን ሥራ ሁሉ በዋግና በአረማሞ መታሁ፤ ያም ሆኖ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም - ይህ የያህዌ ዐዋጅ ነው።
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 18 \v 19 18 ከዚህ ቀን ጀምሮ ማለትም የያህዌ ቤተመቅደስ መሠረት ከተጣለበት ከዘጠነኛው ወር ሃያ አራተኛው ቀን ጀምሮ ወደፊት ቁጠሩ፤ ልብ አድርጋችሁ አስቡት! 19 በጎተራው የቀረ ዘር ይኖራልን? የወይኑና የበለሱ፣ የሮማኑና የወይራው ዛፍ ፍሬ አላፈሩም! ከዚህ ቀን ጀምሮ እባርካችኋለሁ!”
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 20 \v 21 \v 22 20 በዘጠነኛው ወር በወሩም ሃያ አራተኛ ቀን የያህዌ ቃል በድጋሚ ወደ ሐጌ መጣ፤ እንዲህም አለ፣ 21 “ለይሁዳ ገዥ ለዘሩባቤል እንዲህ በለው፤ “ሰማያትንና ምድርን አናውጣለሁ።
|
||||
22 የመንግሥታትን ዙፋን እገለብጣለሁ፤ የሕዝቦችን መንግሥት ብርታት አጠፋለሁ! ሰረገሎችንና በላያቸው ያሉትን እገለብጣለሁ፤ ፈረሶችና ጋላቢዎቻቸውን በገዛ ወንድሞቻቸው ሰይፍ ይወድቃሉ።
|
Loading…
Reference in New Issue