\c 9 \v 1 ጌታን በመሠዊያው አጠገብ ቆሞ አየሁት፥ እንዲህም አለ፦«መሠረቶቹ እንዲናወጡ የአምዶቹን የላይኛውን ጫፍ ምታ። በራሶቻቸው ሁሉ ላይ ሰባብራቸው፥ ከእነርሱም የቀሩትን በሰይፍ እገድላለሁ። ከእነርሱ ማንም አያመልጥም፥ ማንም አይተርፍም። \v 2 ቆፍረው ወደ ሲዖል ቢወርዱም፥ እጄ ከዚያ ታወጣቸዋለች። ወደ ሰማይ ቢወጡም፥ ከዚያ አወርዳቸዋለሁ።