1 line
1.1 KiB
Plaintext
1 line
1.1 KiB
Plaintext
\v 17 ኤልሳዕ ‹‹የምሥራቁን መስኮት ክፈት›› አለ፤ ንጉሡም ከፈተው፤ ኤልሳዕም ‹‹ፍላጻውን አስፈንጥር!›› አለው፤ ንጉሡም ፍላጻውን እንዳስፈነጠረ ወዲያውኑ ኤልሳዕ፣ ‹‹ፍላጻ ነህ፤ በአንተም አማካይነት እግዚአብሔር ሶርያውያንን ድል ያደርጋል፤ ሶርያውያንን ድል እስክትነሣቸው ድረስ በአፌቅ ከተማ ትወጋቸዋለህ፡፡›› \v 18 ከዚህም በኋላ ኤልሳዕ ንጉሡን ‹‹ሌሎቹንም ፍላጻዎች አንሥተህ በእነርሱ ምድርን ምታ!›› አለው፡፡ ንጉሡም ምድርን ሦስት ጊዜ መትቶ አቆመ፡፡ \v 19 ይህም ኤልሳዕን አስቆጣው፤ ስለዚህም ንጉሡን ‹‹አምስት ወይም ስድስት ጊዜ መተህ ቢሆን ኖሮ በሶርያውያን ላይ ፍጹም ድልን ትቀዳጅ ነበር፤ አሁን ግን ሦስት ጊዜ ብቻ ድል ትነሣቸዋለህ›› አለው፡፡ |